JW subtitle extractor

ስለ ይሖዋ ምሥክሮች ማወቅ ትፈልጋለህ?

Video Other languages Share text Share link Show times

ስለ ይሖዋ ምሥክሮች ማወቅ ትፈልጋለህ?
የተለያየ ዘርና ቋንቋ ያለን ቢሆንም
የምናምንበት ነገርና
ዓላማችን ተመሳሳይ ነው።
የምናመልከው ስሙ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተገለጸውንና
የሁሉም ነገሮች ፈጣሪ የሆነውን ይሖዋን ነው።
ክርስቲያኖች ስለሆንን፣
የኢየሱስ ክርስቶስን ትምህርቶችና ምሳሌዎች እንከተላለን።
እንደ ኢየሱስ ሐቀኛና ሰላማዊ ለመሆን ጥረት እናደርጋለን፤
እንዲሁም የምንኖርበትን አገር ሕግ እናከብራለን።
የኢየሱስን ምሳሌ የምንከተልበት ዋነኛው መንገድ
ሰዎች ስለ መጽሐፍ ቅዱስና
ስለ አምላክ መንግሥት እንዲማሩ መርዳት ነው።
የይሖዋ ምሥክሮች ተብለን የምንጠራው
ስለ ይሖዋ አምላክና ስለ መንግሥቱ
ስለምንመሠክር ወይም ስለምንናገር ነው።
ስለ አምላክና ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ለመማር
በየሳምንቱ በስብሰባ አዳራሾቻችን እንሰበሰባለን።
በስብሰባው ላይ ሁሉም ሰው መገኘት ይችላል፤
መግቢያ በነፃ ነው።
አንተም በስብሰባዎቻችን ላይ እንድትገኝ እንጋብዝሃለን።
በአቅራቢያህ የሚገኘውን የስብሰባ አዳራሽ ለማወቅ
አንድ የይሖዋ ምሥክር ማነጋገር
ወይም በjw.org ላይ የሚገኘውን
የስብሰባ መፈለጊያ መጠቀም ትችላለህ።