JW subtitle extractor

ማርክ ኑሜር፦ ሁለት ዓይነት ግያዞች—158ኛው የጊልያድ ምረቃ

Video Other languages Share text Share link Show times

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሶ የምናገኘው
አንድ ግያዝ ብቻ ነው።
የኤልሳዕ አገልጋይ የሆነው ግያዝ።
የይሖዋ ነብይ የነበረው ኤልሳዕ
በግለሰብ ደረጃ ልዩ ሥልጠና ሰጥቶታል።
ነብዩ ኤልሳዕ ይበልጥ ታዋቂ ሲሆን፣
አክብሮት ሲያተርፍ፣
ግያዝም አገልጋዩ ስለሆነ
በብዙዎች ዘንድ
ተጨማሪ ክብር አግኝቶ እንደሚሆን ግልጽ ነው።
ሌሎች የሚያከብሩት፣
በእንግድነት የሚቀበሉት ሰው ሆኗል።
ይህን ያገኘው ግን በራሱ ሳይሆን
የኤልሳዕ አገልጋይ ስለሆነ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መጀመሪያ ላይ የተጠቀሰው ግያዝ
ታማኝ፣ ሐቀኛና የሰውን ስሜት የሚረዳ ነው።
ግን ሁለተኛ ነገሥት ስለ ግያዝ
ፈጽሞ ተቃራኒ ዘገባም ይዟል።
እንዲያውም ዘገባዎቹን ስናነብ
ሁለት ግያዞች የነበሩ ነው የሚመስለው።
ምን ተፈጥሮ ነው?
እኛስ ከዘገባው ምን ትምህርት እናገኛለን?
እስቲ ዘገባውን እንመልከት።
ስለ ግያዝ ለመጀመሪያ ጊዜ የምናነበው
በሁለተኛ ነገሥት ምዕራፍ 4 ላይ ነው።
ዘገባው አንዲት ታዋቂ ሹነማዊት ሴት
ለኤልሳዕ ልዩ አቀባበል እንዳደረገችለት ይነግረናል።
ምግብና የሚያርፍበት ቦታ አዘጋጅታለታለች።
ኤልሳዕ ሹነማዊቷ ላደረገችለት ነገር ሁሉ
አድናቆቱን ገልጿል።
እስቲ መጽሐፍ ቅዱሳችንን አውጥተን
ዘገባውን ከዚያ ጀምረን እንመርምር።
ሁለተኛ ነገሥት ምዕራፍ 4
ቁጥር 13 እንዲህ ይላል፦
“ከዚያም ኤልሳዕ ግያዝን እንዲህ አለው፦
“‘እባክህ [ሹነማዊቷን] እንዲህ በላት፦
“እንግዲህ ለእኛ ስትዪ ብዙ ተቸግረሻል።
[ለአገልጋዩ ለግያዝም ጭምር ማለት ነው።]
“ታዲያ ምን እንዲደረግልሽ ትፈልጊያለሽ?
“ንጉሡን ወይም የሠራዊቱን አለቃ
የማነጋግርልሽ ነገር አለ?’”
“እሷ ግን ‘እኔ እኮ የምኖረው
በገዛ ወገኖቼ መካከል ነው’ ብላ መለሰች።”
በሌላ አባባል
አታስብ። ምንም አልጎደለብኝም።
የሚያስፈልገኝ ሁሉ አለኝ።
ሀብት ንብረት አለኝ።
ጥሩ ባል አለኝ።
ሁሉ ነገር አለኝ።
ማለቷ ነበር።
ቁጥር 14
ግያዝ ስለ ሴትየዋ
ያስተዋለው አንድ ነገር እንደነበር ይነግረናል።
ያቺ ሀብታም ሴት
የጎደላትን አንድ ነገር አስተውሏል።
ለኤልሳዕም ቁጥር 14 ላይ ነግሮታል።
እንዲህ አለው፦ “ወንድ ልጅ የላትም።”
ግያዝ ሴትየዋ የጎደላትን
ማለትም ልጅ እንደሌላት ማስተዋል ችሏል።
ይህ ደግሞ ግያዝ
በጣም አስተዋይ ሰው እንደነበር የሚጠቁም ነው።
የሰዎችን ችግር የሚረዳና
አሳቢ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።
ግያዝ ከራሱ ይልቅ የሌሎች ሰዎች ጉዳይ የሚያሳስበው
ለጋስና ሰዎችን መርዳት የሚወድ ሰው ነበር።
ደስ የሚል ባሕርይ ነበረው።
በአምላክ ላይ ጠንካራ እምነት እንዳለውም ይጠቁማል።
ምክንያቱም ኤልሳዕ ሴትየዋን ሊረዳት እንደሚችል እርግጠኛ ነበር።
ኤልሳዕም የግያዝን ምክር በመስማት
ሴትየዋን ቁጥር 16 ላይ እንደምንመለከተው
“‘የዛሬ ዓመት በዚሁ ጊዜ ወንድ ልጅ ትታቀፊያለሽ’ አላት።”
ሴትየዋ ፈጽሞ አገኘዋለሁ ብላ ያላሰበችው ነገር ነው።
ግን በቀጣዩ ዓመት ይሖዋ
ወንድ ልጅ በመስጠት ባረካት።
ከዚህ ዘገባ እኛም ትምህርት እናገኛለን።
የበላይ ተመልካቾች ባንሆንም እንኳ
ይሖዋ ለመልካም ሥራ ይጠቀምብናል።
ምናልባት አንዳንዴ
የሆነ ዓይነት ሐሳብ ታቀርቡ ይሆናል።
ሐሳቡም ጥሩ ውጤት አመጣ እንበል።
ግን ሐሳቡ የእናንተ እንደሆነ አልታውቀም።
ያጋጥማል።
እውቅና ባይሰጣችሁም አትዘኑ።
ይሖዋ ሐሳባችሁን ጥሩ እንዲያመጣ
ስለባረከው ተደሰቱ።
ራሳችሁን
‘ያገኘሁትን ሥልጠናና ጥልቅ ማስተዋል የምጠቀመው
ሌሎችን ለመርዳት ነው?
ወይስ ትኩረት ወደ ራሴ ለመሳብ?’ ብላችሁ ጠይቁ።
እስቲ ወደ ዘገባው ተመልሰን ቀጥሎ የሆነውን እንመልከት።
ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ
ያ ልጅ ሞተ።
በዚህ የመከራዋ ወቅት
ሹነማዊቷ ሴት የኤልሳዕ እርዳታ አስፈለጋት።
እጅግ ከባድ በሆነ
ልብ በሚሰብር ሀዘን ተደቁሳ
ወደ ኤልሳዕ መጥታ እግሩ ላይ ተደፋች።
በዚህ ወቅት
በግያዝ ልብ ውስጥ
መጥፎ ባሕርያት ማቆጥቆጥ እንደጀመሩ
ፍንጭ እናገኛለን።
ሁለተኛ ነገሥት ምዕራፍ 4
ቁጥር 27 እንደሚነግረን
ልቧ ተሰብሮ ኤልሳዕ እግር ላይ ስትጠመጠም
ግያዝ አጽናናት?
በጭራሽ!
እንዲያውም ግያዝ
ሊያስለቀቃት መጣ።
በኃይል ሊያስለቅቃት ሞከረ።
ሹነማዊቷን ሴት
ያቺን ወዳጃቸውን፣
እንግዳ ተቀባይዋን፣
ለእሱም ሆነ ለኤልሳዕ ለዓመታት
ልዩ ደግነት ስታሳይ የቆየችውን ሴት
እርዳታ በሚያስፈልጋት
በጣም ባዘነችበት ወቅት
ግያዝ ጨከነባት።
ምናልባት ግያዝ ድርጊቷ
የኤልሳዕን ክብር ዝቅ እንደሚያደርግ
ተሰምቶት ይሆን?
ኤልሳዕ ግን ፈጽሞ እንደዛ አልተሰማውም።
እንዲያውም ቁጥር 26 ላይ
ከሩቅ እንዳያት
ግያዝ ሂድና “ምነው፣ ደህና አይደለሽም?”
“ልጁስ ደህና አይደለም?”
ብሎ እንዲጠይቃት ልኮታል።
በጣም የሚገርመው
ግያዝ ሲጠይቃት “ሁሉም ነገር ደህና ነው”
ብላ መመለሷ ነው።
ምናልባት ግያዝ እንደቀድሞው አለመሆኑን
አስተውላ ሊሆን ይችላል።
ግያዝ ምን ነካው?
ያ የሰዎችን ስሜት የሚረዳው፣
አሳቢ የሆነው ግያዝ የት ገባ?
ምናልባት እምነቱ ተዳክሞ ወይም
ለነበረው መብት ያለው አድናቆት ቀንሶ ይሆን?
መጀመሪያ ላይ የነበረውን ደስታ አጥቶ
ወይም በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ሥራ ስለሠራ
ተሰላችቶ ይሆን?
በየቀኑ ከኤልሳዕ ጋር ስለሚሆን
ኤልሳዕ የነበሩትን አንዳንድ ጉድለቶች መመልከቱ
አበሳጭቶት ይሆን?
ሊሆን ይችላል።
ወይስ የኤልሳዕ አገልጋይ ከመሆን ባለፈ
ተጨማሪ መብት ማግኘት ፈልጎ ይሆን?
ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን
የሆነ ወቅት ላይ
አመለካከቱና ስሜቱ ተቀይሯል።
ለረጅም ጊዜ ኤልሳዕን ሲያገለግል የነበረው
እምነት የሚጣልበት ግያዝ ደብዝዞ
አዲስ ግያዝ
ብቅ ማለት ጀምሯል።
ከዚህ ትልቅ ትምህርት እናገኛለን።
ሌሎችን ከማገልገል የበለጠ
ክብራችን እያሳሰበን ከመጣ
አደጋ ውስጥ ነን።
ርኅራኄ ማሳየት ካቃታችሁ
የአገልግሎት መብታችሁ፣
ኃላፊነታችሁ ትርጉም የለውም።
እርዳታችሁ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች የምትመለከቱት
እንደ ሸክም ነው ወይስ
እንደ ውድ የይሖዋ በግ?
ግያዝ ምዕራፍ 4 ላይ ያሳየው ምግባር
አስገርሟችሁ ይሆናል።
ግን ምዕራፍ 5 ላይ
ጭራሽ ዓይኑን በጨው አጥቦ ሊመጣላችሁ ነው።
ሊለይለት ነው።
ምዕራፍ 5 ቁጥር 20 ላይ
ግያዝ ንዕማንን “ሶርያዊው” ብሎ ጠርቶታል።
ይህን ሰው ሌላ ዘር ስላለው ብቻ ንቆታል።
ቢያጭበረብረውም ችግር እንደሌለው ተሰምቶታል።
ከዚያም ንዕማንን ዋሽቶ
ኤልሳዕ አልቀበልም ያለውን ስጦታ ወስዷል።
ለጋሱ ግያዝ ተቀይሮ
ስግብግቡ ግያዝ ሆነ።
ያሳዝናል።
ግን በዚህ ብቻ አላበቃም።
ቁጥር 25 ላይ
ኤልሳዕን ዋሽቷል።
ኤልሳዕ ግያዝን “ከየት ነው የመጣኸው?”
ብሎ ሲጠይቀው።
“ኧረ አገልጋይህ የትም አልሄደም” አለ።
ግያዝ
ምን ነካው?
የአምላክን ነብይ መዋሸት
በጣም ሊያስፈራው ይገባ ነበር።
የዋሸው አንድን ተራ ሰው ሳይሆን
የይሖዋን ነብይ ነው።
ነብዩ በይሖዋ እርዳታ
ሌሎች የማያውቋቸውን ነገሮች ማወቅ
እንዲሁም ተዓምራትን መፈጸም ይችል ነበር።
እሱን እንዴት ይዋሻል?
ግያዝ
ኤልሳዕን ማታለል እንደሚችል ማሰቡ በራሱ
የሚገርም ነው።
መጀመሪያ ላይ የምናውቀው ግያዝ
አሁን ተቀየረ።
ለጋስ ከመሆን ይልቅ ስስታም
ታማኝ ከመሆን ይልቅ ውሸታም ሆነ።
ታዲያ አዲሱ ግያዝ
መጨረሻው ምን ሆነ?
ቁጥር 27 ኤልሳዕ ያለውን ይነግረናል።
“ስለሆነም የንዕማን የሥጋ ደዌ
በአንተና በዘርህ ላይ ለዘላለም ይጣበቃል።”
ይሖዋ ‘ገንዘቡን ወስደሃል አይደል?
በሽታውንም አብረህ ውሰድ’ ያለው ያህል ነው።
እንዴት ያሳዝናል።
አሁን ሰዎች የሚጠሩት ‘የነብይ አገልጋይ’
ብለው ሳይሆን
‘ለምጻሙ ግያዝ’ ብለው ነው።
ግን እንደ እናንተ ካሉ
ጎልማሳና ታማኝ የይሖዋ አገልጋዮች ጋር
ስለ ግያዝ የምናውራው ለምንድን ነው?
ግልጽ ላደርግላችሁ የምፈልገው
ግያዝ ያንጸባረቃቸውን እነዚያን መጥፎ ባሕርያት
በእናንተ ውስጥ ፈጽሞ አላየንም።
ከዚህ ይልቅ እናንተ
እምነት የሚጣልባችሁ
ትጉ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ናችሁ።
በየዕለቱ ለትምህርቱ
በደንብ ተዘጋጅታችሁ ትመጡ ነበር።
ደግና አፍቃሪ ናችሁ።
እንዲሁም ለይሖዋና ለድርጅቱ
ታማኝ እንደሆናችሁ አስመሥክራችኋል።
ያም ቢሆን ግን
በጣም ስለምንወዳችሁ
በግያዝ ላይ የደረሰው
በእናንተ ላይ ፈጽሞ እንዳይደርስ
ለማሳሰብ ነው።
በግያዝ ላይ የደረሰው ነገር
ለሁላችንም ማስጠንቀቂያ ይሆነናል።
በይሖዋ አገልግሎት የተጠመድን ብንሆንም
እንዲህ ዓይነት ነገር ሊያጋጥመን ይችላል።
ግያዝ የተሰጠውን ትልቅ ኃላፊነት እየተወጣም
ባሕሪው ተቀይሯል።
በእሱ ላይ የደረሰው
በእኛ ላይ እንዲደርስ
ፈጽሞ መፍቀድ የለብንም።
ግያዝ ይሖዋ የሰጠውን ሥራ ማከናወኑን አላቆመም።
ግን አድናቆቱ እየቀነሰ መጣ።
ምን እንማራለን?
ላሉን የአገልግሎት መብቶች
ሁልጊዜም አድናቆት ይኑረን።
ሁላችንም እንደ መጀመሪያው
እንደ ታማኙ ግያዝ እንሁን።
ምናልባት አንዳንድ ጊዜ ሥራችሁ
ያን ያህል አስፈላጊ የማይመስል
ትንሽ የሚያሰለች ወይም
ተደጋጋሚ ሊሆን ይችላል።
ግን ችግር የለውም።
ምክንያቱም ሌሎች ሳያዩን
በስውር
ያሳየነው እምነት
የላቀ ዋጋ አለው።
ለመታየት ብላችሁ ምንም ነገር አታድርጉ።
ሁሉን ነገር ይሖዋን ለማወደስና
ለማስደሰት አድርጉት።
ሁልጊዜም
የይሖዋን ታማኝ ፍቅርና በረከቶች
በሚገባ እንድታጣጥሙ
በዚህ ንግግር ላይ የጠቀስናቸውን
ሁለቱን ግያዞች አስታውሱ።