JW subtitle extractor

የት ናቸው? ሮሳሊያ ፊሊፕስ፦ ዳግም እንደማገኘው ተስፋ ተሰጥቷል

Video Other languages Share text Share link Show times

የተወለድኩት ታዋቂ ዘፋኞችና ተዋንያን ካሉበት ቤተሰብ ነው።
በጣም ዝነኛው አባቴ ይመስለኛል።
ኸርማን ቫልዴስ ይባላል።
በአብዛኛው የሚታወቀው ግን ቲንታን ተብሎ ነው።
ሙዚቃ ሕይወቴ ነበር።
ከልጅነቴ ጀምሮ ስሜቴን የምገልጸው በሙዚቃ ነበር።
የሆነ ነገር ሲሰማኝ ጊታሬን አንስቼ ሙዚቃ አቀናብራለሁ።
ሙዚቃን እንደ ሥራ እይዘዋለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም።
የምፈልገው ያን አልነበረም።
ሆኖም የ 15 ዓመት ልጅ እያለሁ አባቴ ሞተ።
ስለዚህ ቤተሰባችንን በገንዘብ ለመደገፍ ሥራ መያዝ ነበረብኝ።
አንድን የሙዚቃ ቡድን ተቀላቀልኩ።
ከዚያም ታዋቂ ተዋናይና ዘፋኝ ሆንኩ።
ከጊዜ በኋላ አብሬያቸው የምሠራቸው ሰዎች
ጥሩ ሥነ ምግባር እንደሌላቸው ተገነዘብኩ።
ስለሆነም በሰዎች ላይ እምነት መጣል አቃተኝ።
እውነትን ስማር ግን ቅን ከሆኑ፣
እኔን ከልብ ከሚወዱኝና ደስ ከሚሉ ሰዎች ጋር ተገናኘሁ።
ከዚያ እኔም መለወጥ ጀመርኩ።
በቃ የተለየ ሰው ሆንኩ።
ደስተኛ፣ ፍልቅልቅና ተጫዋች ሰው ሆንኩ።
ወላጅ እንደመሆናችን መጠን
ወደ ሜክሲኮ ስንመለስ በዋነኝነት ያሳሰበን ነገር
‘ልጆቻችን በመዝናኛው ዓለም ተስበው ወደዚያ ቢገቡስ’ የሚለው ነበር።
እኔና ባለቤቴ ልጆቻችን እንዲህ ያለ ነገር እንዳያጋጥማቸው
የተቻለንን ሁሉ አድርገናል።
በአንድ ወቅት ሜክሲኮ ሲቲ ውስጥ
ከአንድ ታዋቂ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ቀጠሮ ነበረኝ።
ወደዚያ የሄድኩት ከ 17 ዓመቷ ልጄ ከጂያና ጋር ነበር።
እዛም ጥሩ ችሎታ ያላቸውን ሰዎች እየፈለገ የሚቀጥር አንድ ሰው አያት።
‘አንቺም ትዘፍኛለሽ’ ሲላት
‘አዎ’ አለችው።
ስትዘፍን ሰማትና ድምጿን በጣም ወደደው።
ስለዚህ ወዲያውኑ ወደ ቢሮ ወሰዳትና እንድትቀመጥ ጋበዛት።
እንዲህ ሲላት ሰማሁ፦
‘እየውልሽ እዚህ የቴሌቪዥን ጣቢያ ውስጥ ሥራ እንቀጥርሻለን።
‘ታዋቂ ሰው እናደርግሻለን።
‘ኮንትራት አዘጋጅልሻለሁ።
ሰኞ መጥተሽ እንፈራረማለን።’
ጂያና ከቢሮው ስትወጣ በጣም ፈርቼ ነበር።
ከዚያም “ግብዣውን ተቀበልሽ?” አልኳት።
እሷም እንዲህ አለችኝ፦
“ኧረ በፍጹም እማዬ።
“ከምንም ነገር በላይ የሚያስደስተኝ ይሖዋን ማገልገል ነው።
የአቅኚነት አገልግሎቴን በጣም ነው የምወደው” አለችኝ።
በጣም የሚያስገርመው ከአንድ ሳምንት በኋላ
ቤቴል ውስጥ በአንድ የሙዚቃ ፕሮጀክት ውስጥ
እንድትካፈል የሚጋብዝ ደብዳቤ ደረሳት።
ያንን የሚያምረውን ድምጿን ይሖዋን ለማወደስ ተጠቀመችበት።
አሁንም በፕሮጀክቶች ላይ ትካፈላለች።
ላለፉት በርካታ ዓመታት
ይሖዋ ለእኔና ለልጄ ቤቴ ውስጥ
በሙዚቃ ፕሮጀክቶች ውስጥ የመካፈል መብት ሰጥቶናል።
ሰይጣን ትኩረቴን በተለያዩ ነገሮች ለመከፋፈል ይሞክራል።
ለምሳሌ በአንድ ወቅት አባቴን በሚዘክር ሥራ ላይ
እንድካፈል ኮንትራት ቀረበልኝ።
ሥራው በጣም ጊዜዬን የሚወስድ ነበር።
በእርግጠኝነት የዘወትር አቅኚነቴንም ይነካብኛል።
ስለዚህ ሥራውን እምቢ አልኩኝ።
ባለፉት ዓመታት ሁሉ ይሖዋ እኔን መባረኩን አላቋረጠም።
አንድ ዓይነት የሥራ ግብዣ ቀርቦልኝ እንቢ ስል
ይሖዋ ከዚያ የበለጠ ነገር ይሰጠኝ ነበር።
ለምሳሌ በተለያዩ ቲኦክራሲያዊ ትምህርት ቤቶች የሚካፈሉ ወንድሞችን
የማስተናገድ መብት አግኝቻለሁ።
ያጋጠሙኝ ተፈታኝ ነገሮች በይሖዋ መታመንን አስተምረውኛል።
ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው ‘ያለ እምነት አምላክን ደስ ማሰኘት አይቻልም።
ደግሞም አምላክ ከልብ ለሚፈልጉት ወሮታ ከፋይ ነው።’
ከእናቴ ጋር ማገልገል በጣም ያስደስተኛል።
አሁን ከ90 ዓመት በላይ ሆኗታል።
በተለያዩ የአገልግሎት መስኮች መካፈል ያስደስተናል።
ባለፉት ዓመታት ውስጥ በርካታ ዘመዶቼ መጽሐፍ ቅዱስን እንዳስጠናቸው ጠይቀውኛል።
አንዳንዶቹ የይሖዋ ምሥክሮች ሆነዋል።
ከእናቴና ከልጄ ጋር ሆነን ጊታር እየተጫወትን ስንዘምር በጣም ደስ ይለኛል።
ከወንድሞችና ከእህቶች ጋር ሰብሰብ ብለን አስደሳች ጊዜ እናሳልፋለን።
በአዲሱ ዓለም አባቴን የማይበትን ጊዜ በጉጉት እጠባበቃለሁ።
እቅፍ አድርጌ እቀበለዋለሁ።
ልጆቼን አስተዋውቀዋለሁ።
ከእናቴም ጋር አብረው ይሆናሉ።
አባቴ የሚነሳው
ባሕር ዳርቻ አካባቢ ይመስለኛል።
ድሮ እንደምናደርገው አብረን እንድንዘምር እፈልጋለሁ።
በግሌ ያደረኩት ውሳኔ ለዘላለም ለይሖዋ ታማኝ ሆኖ መኖር ነው።