JW subtitle extractor

‘ብረት ብረትን ይስላል’—ደግነት

Video Other languages Share text Share link Show times

ሰላም! ጆናታን እባላለሁ።
ይህ ብረት ብረትን ይስላል ፕሮግራማችን ነው።
ዛሬ ስለ ደግነት እንነጋገራለን።
ኢየሱስ ደግ ስለነበር
ኃጥያተኞች፣
ሕመምተኞች፣
ልጆችም ጭምር ይቀርቡት ነበር።
ኢየሱስ
ልክ ይሖዋ ደግነት አሳይቷል።
ለጥሩም ሆነ ለክፉ ሰዎች።
ኢየሱስ ደግነት ያሳየው
ደግ ለነበሩ ወይም
ለእሱ ጥሩ አመለካከት ላላቸው ሰዎች ብቻ አልነበረም።
ኢየሱስ ሁልጊዜም
ደግነት ያሳይ ነበር።
ምክንያቱም
በሰዎች ላይ ምን ያህል በጎ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር
እንዲሁም ይሖዋን እንደሚያስከብር ያውቃል።
እኛስ ግን
ደግነት ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው?
የታካሚው መጠየቂያው ሰዓት አልፏል።
ሁላችሁም ውጡ!
ውይ በጣም ይቅርታ
ጊዜ ያለን መሎኝ ነበር።
አምስት ደቂቃ እኮ አለን።
ግድ የለም እንሂድ።
ቶሪ፣ ሌላ ጊዜ መጥተን ደግሞ እንጠይቅሻለን።
እህት ጥሩ እርምጃ ወስዳለች
ከጓደኞቿ ጋር ሆና ክፍሉን ለቅቃ ወጥታለች።
ምንም እንኳ ተጨማሪ ጊዜ ቢኖራትም።
ግን ሌላስ ምን ማድረግ ትችላለች?
ደግነት ለማሳየት የሚረዳን የመጀመሪያው ነገር
ስሜታቸውን መረዳት ነው።
እራሳችንን የማነጋግረው ሰው
በምን ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ነው?
ምን ያስፈልገዋል?
ብለን እንጠይቅ።
ከዚያ በትኩረት በማዳመጥ
እንደምናስብላቸው እናሳይ።
እ. . አንዴ መጣሁ።
እደርስባችኋለሁ።
ታዲያስ
ሰላም።
ጓደኛዬን በሚገባ እየተንከባከብሻት ስለሆነ
በጣም አመሰግንሻለሁ።
ሥራዬ ነው።
ይቅርታ ቅድም ቅር ካሰኘኋችሁ።
በጣም ሥራ በዝቶብናል።
በቂ ሰው ደግሞ የለንም።
አመሰግናለሁ ማለታችን ብቻ እንኳ
ትልቅ ለውጥ ያመጣል።
ለነርሷ ትልቅ ትርጉም ነበረው።
ሰዎች ስሜታቸውን አውጥተው ሲነግሩን
በፍቅርና በአክብሮት ልናነጋግራቸው እንፈልጋለን።
ሁለተኛው ነጥብ ይሄ ነው።
ለሰዎች ከልባችን የምናስብ ከሆነ
በንግግራችን ላይ መታየቱ አይቀርም።
ቃላታችንንም ሆነ
የምንናገርበትን መንገድ እንመርጣለን።
ቅር እንዳናሰኛቸው እንጠነቀቃለን።
ይቅርታ፣ በጣም ሥራ በዝቶብናል።
በቂ ሰው ደግሞ የለንም።
ኸረ ምንም አላጠፋሽም።
ሥራችሁ ውስጣዊ እርካታ የሚያስገኝ ቢሆንም
አንዳንዴ ከባድ እንደሚሆን እገምታለሁ።
አዎ ዛሬም ከባድ ቀን ነበር።
ቢያንስ ግን ሻይ መጠጣትሽ ጥሩ ነው።
አይ. . እሱማ ተደፋብኝ
ሌላ ለማምጣት ደግሞ ጊዜ አጣሁ።
ውይ. . በጣም አስቸጋሪ ቀን ነዋ ያሳለፍሽው።
አዎ።
ማንዲ እባላለሁ።
ሜሪ፣ አመሰግጋለሁ።
በቃ ቻው፣ ሥራ አላስፈታሽ።
ግሩም ምሳሌ ነው ያየነው።
የነርሷን ስሜት ቀይራዋለች።
ነርሷ ያለችበትን ሁኔታ ካወቀች በኋላ
ሌላስ ምን ማድረግ ትችላለች?
ይህ ወደ ሦስተኛው ነጥብ ይመራናል።
ደግነት አሳቢነት ከማሳየት
ወይም ከንግግር ባለፈ
በተግባር መደገፍ አለበት።
ሰዎችን የምንረዳበት አጋጣሚ ለማግኘት
ጥረት እናደርጋለን።
ጊዜያችንን፣ ገንዘባችንን ወይም ጉልበታችንን
መስዋዕት ማድረግ ቢጠይቅም
ፈጽሞ የሚያስቆጭ ነገር አይደለም።
እ. . ሜሪ እንቺ።
ውይ. . ለምን ተቸገርሽ!
ኸረ ችግር የለውም።
አድናቆቴን ለመግለጽ ነው።
በጣም ነው የማመሰግነው።
እ. . አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ?
እሺ።
ልትጠይቂያት የመጣሽው ሴት ማን ናት?
ሊጠይቋት የሚመጡት ብዙ ናቸው።
የቅርብ ጓደኛችን ነች።
ቤተሰብ በያት።
የይሖዋ ምሥክሮች ነን።
እ. . .
የእናንተ ሰዎች ደጎች ናቸው።
እናመሰግናለን።
ብታይ ቶሪ በጣም ጥሩ ጓደኛዬ ነች።
የምናሳየው ደግነት
ከልብ የመነጨ ሊሆን ይገባል።
ደግነት የምናሳየው ሰዎችን ስለምንወድ እንጂ
ለመስበክ ብቻ ብለን አይደልም።
እርግጥ
ሰዎች እንደምናስብላቸው ሲያውቁ
ጥሩ ምላሽ ይሰጣሉ።
እስቲ እንከልሰው
ደግነት ለማሳየት
ሦስት እርምጃዎች መውሰድ እንችላለን።
አንደኛ፣ ስሜታቸውን መረዳት።
ስለሚያሳስባቸውና ስለሚያስፈልጋቸው ነገር እናስብ።
ስሜታቸውን ሲገጹ
እናዳምጥ።
ሁለተኛ፣ በፍቅርና በአክብሮት ማነጋገር።
እንደምናስብላቸው ከቃላታችንና
ከምንናገርበት መንገድ ማስተዋላቸው አይቀርም።
ሦስተኛ፣ በድርጊታችን እናሳይ።
ሰዎችን ለመርዳት አጋጣሚዎችን እንፈልግ።
እንዲህ ስናደርግ
የመስበክ አጋጣሚ እናገኝ ይሆናል።
ግን አስታውሱ ከምንም በላይ የሚያስፈልገን ነገር
ልክ እንደ ኢየሱስ ሰዎችን መውደድ ነው።
ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ
“ፍቅር ደግ ነው” ይላል።