JW subtitle extractor

መጽሐፍ ቅዱስን መማር የሚኖርብን ለምንድን ነው?—ሙሉው ቪዲዮ

Video Other languages Share text Share link Show times

አፍ ከፈታንበት ጊዜ አንስቶ ጥያቄዎችን እንጠይቃለን።
ሰማዩ መጨረሻው የቱ ጋ ነው?
ኮከቦች የሚያበሩት ለምንድን ነው?
መጥፎ ነገር በሰዎች ላይ የሚደርሰው
ለምንድን ነው?
የመጣነው ከየት ነው?
የምንሞተው ለምንድን ነው?
ሰዎች መልስ ለማግኘት
ያላደረጉት ጥረት የለም።
የአሁኑን ያህል መረጃ እንደ ልብ
የሚገኝበት ዘመን ኖሮ አያውቅም።
ሆኖም ሕይወትን፣ መከራንና ሞትን
አስመልክቶ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ አልተገኘም።
ታዲያ የእነዚህን አሳሳቢ ጥያቄዎች መልስ
ከየት ማግኘት ይቻላል?
ከመጽሐፍ ቅዱስ ማግኘት ይቻል ይሆን?
ብዙ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ ተረት እንደሆነ፣
ጊዜ እንዳለፈበት
ወይም ለመረዳት ከባድ እንደሆነ ይሰማቸዋል።
ይሁንና ችግሩ ያለው መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ነው?
ወይስ ሰዎች ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ባላቸው ግንዛቤ ላይ?
ብዙዎች ዓለምን የሚገዛው
አምላክ እንደሆነ ይሰማቸዋል።
ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል?
ዓለም ከቁጥጥር ውጭ እየሆነ ነው።
ዓለማችን በመከራና በሥቃይ የተሞላ ነው።
ሕመምና ሞት፣
ድህነትና አደጋ ነግሧል።
ታዲያ አፍቃሪ የሆነ አምላክ
ለዚህ ሁሉ እንዴት ተጠያቂ ሊሆን ይችላል?
የመጽሐፍ ቅዱስን መልስ ስታውቅ
ትገረም ይሆናል።
'መላው ዓለም በክፉው ኃይል ሥር ነው' ይላል።
በሌላ አነጋገር በዓለም ላይ ከሚታዩት ችግሮች በስተ ጀርባ
አንድ ክፉ ኃይል አለ።
ችግሮች እንዲባባሱ የሚያደርገው ይህ ኃይል ነው።
ሰዎች ምንም ያህል ጥረት ቢያደርጉ
ለዓለም ችግሮች መፍትሔ ማግኘት የማይችሉት ለዚህ ነው።
ደስ የሚለው፣ አሁን ያለው ሁኔታ
በዚህ እንደማይቀጥል መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
እዚህ ችግር ውስጥ እንዴት እንደገባን፣
አምላክ የሚያመጣውን መፍትሔና
እስከዚያው ችግሩን መቋቋም የምንችልበትን መንገድ ይነግረናል።
መጽሐፍ ቅዱስ በመላው ዓለም የሚኖሩ ሰዎች
ለሚያሳስቧቸው ጥያቄዎች መልስ ይሰጣል።
አንተስ መልስ ማግኘት ትፈልጋለህ?
መጽሐፍ ቅዱስን መማር ከፈለግክ
የይሖዋ ምሥክሮች በደስታ ይረዱሃል።
ድረ ገጻችን ላይ የሚገኘውን ቅጽ ሞልተህ ከላክህ
አንድ የይሖዋ ምሥክር በሚመችህ ሰዓትና ቦታ
መጽሐፍ ቅዱስን ሊያስተምርህ ይችላል።